• 1. (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
  • 2. (ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
  • 3. ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
  • 4. አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
  • 5. ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
  • 6. «የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
  • 7. ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
  • 8. ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
  • 9. ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
  • 10. «ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
  • 11. ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
  • 12. በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
  • 13. ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
  • 14. በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
  • 15. ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
  • 16. በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
  • 17. (በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
  • 18. ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
  • 19. ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
  • 20. (ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
  • 21. መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
  • 22. ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
  • 23. ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
  • 24. ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
  • 25. በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
  • 26. ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
  • 27. «አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
  • 28. (ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
  • 29. ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
  • 30. በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
  • 31. አላመነምም አልሰገደምም፡፡
  • 32. ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
  • 33. ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
  • 34. የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
  • 35. ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
  • 36. ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
  • 37. የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
  • 38. ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
  • 39. ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
  • 40. ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
ሼር ያድርጉ
logo
logo
logo
logo
logo
  • 1.ورَةُ الْفَاتِحَة
  • 2.ورَةُ البقرة
  • 3.سُورَةُ آل عمران
  • 4.سورة النساء
  • 5.سورۃ المائدة
  • 6.سورة الأنعام
  • 7.سورة الاعراف
  • 8.سورۃ الانفال
  • 9.سورة التوبة
  • 10.سورة يونس
  • 11.سورۃ ھود
  • 12.سورة يوسف
  • 13.سورة الرعد
  • 14.سورة ابراهيم
  • 15.سورة الحجر
  • 16.سورة النحل
  • 17.سورة الإسراء
  • 18.سورة الكهف
  • 19.سورة مريم
  • 20.سورة طه
  • 21.سورة الأنبياء
  • 22.سورة الحج
  • 23.سورة المؤمنون
  • 24.سورة النور
  • 25.سورة الفرقان
  • 26.سورة الشعراء
  • 27.سورة النمل
  • 28.سورة القصص
  • 29.سورة العنكبوت
  • 30.سورة الروم
  • 31.سورة لقمان
  • 32.سورة السجدة
  • 33.سورة الأحزاب
  • 34.سورة سبإ
  • 35.سورة فاطر
  • 36.سورةيس
  • 37.سورة الصافات
  • 38.سورة ص
  • 39.سورة الزمر
  • 40.سورة غافر
  • 41.سورة فصلت
  • 42.سورة الشورى
  • 43.سورة الزخرف
  • 44.سورة الدخان
  • 45.سورة الجاثية
  • 46.سورة الأحقاف
  • 47.سورة محمد
  • 48.سورة الفتح
  • 49.ورة الحجرات
  • 50.سورة ق
  • 51.سورة الذاريات
  • 52.سورة الطور
  • 53.سورة النجم
  • 54.سورة القمر
  • 55.سورة الرحمن
  • 56.سورة الواقعة
  • 57.سورة الحديد
  • 58.سورة المجادلة
  • 59.سورة الحشر
  • 60.سورة الممتحنة
  • 61.سورة الصف
  • 62.سورة الجمعة
  • 63.سورة المنافقون
  • 64.سورة التغابن
  • 65.سورة الطلاق
  • 66.سورة التحريم
  • 67.سورة الملك
  • 68.سورة القلم
  • 69.سورة الحاقة
  • 70.سورة المعارج
  • 71.سورة نوح
  • 72.سورة الجن
  • 73.سورة المزمل
  • 74.سورة المدثر
  • 75.سورة القيامة
  • 76.سورة الانسان
  • 77.سورة المرسلات
  • 78.سورة النبإ
  • 79.سورة النازعات
  • 80.سورة عبس
  • 81.سورة التكوير
  • 82.سورة الإنفطار
  • 83.سورة المطففين
  • 84.سورة الإنشقاق
  • 85.سورة البروج
  • 86.سورة الطارق
  • 87.سورة الأعلى
  • 88.سورة الغاشية
  • 89.سورة الفجر
  • 90.سورة البلد
  • 91.سورة الشمس
  • 92.سورة الليل
  • 93.سورة الضحى
  • 94.سورة الشرح
  • 95.سورة التين
  • 96.سورة العلق
  • 97.سورة القدر
  • 98.سورة البينة
  • 99.سورة الزلزلة
  • 100.سورة العاديات
  • 101.سورة القارعة
  • 102.Aسورة التكاثر
  • 103.سورة العصر
  • 104.سورة الهمزة
  • 105.سورة الفيل
  • 106.سورة قريش
  • 107.سورة الماعون
  • 108.سورة الكوثر
  • 109.سورة الكافرون
  • 110.سورة النصر
  • 111.سورة المسد
  • 112.سورة الإخلاص
  • 113.سورة الفلق
  • 114.سورة الناس