• 1. አል-ረሕማን፤
  • 2. ቁርኣንን አስተማረ፡፡
  • 3. ሰውን ፈጠረ፡፡
  • 4. መናገርን አስተማረው፡፡
  • 5. ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
  • 6. ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
  • 7. ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
  • 8. በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
  • 9. መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
  • 10. ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
  • 11. በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
  • 12. የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
  • 13. (ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 14. ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
  • 15. ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
  • 16. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 17. የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
  • 18. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 19. ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
  • 20. (እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
  • 21. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
  • 22. ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
  • 23. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 24. እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
  • 25. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 26. በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
  • 27. የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
  • 28. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 29. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
  • 30. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
  • 31. እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
  • 32. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 33. የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
  • 34. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 35. በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
  • 36. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 37. ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
  • 38. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 39. በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
  • 40. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 41. ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
  • 42. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
  • 43. ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
  • 44. በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
  • 45. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 46. በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
  • 47. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 48. የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
  • 49. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 50. በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
  • 51. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 52. በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
  • 53. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 54. የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
  • 55. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 56. በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
  • 57. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 58. ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
  • 59. ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 60. የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
  • 61. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 62. ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
  • 63. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
  • 64. ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
  • 65. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 66. በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
  • 67. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 68. በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
  • 69. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 70. በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
  • 71. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 72. በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
  • 73. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 74. ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
  • 75. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
  • 76. በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
  • 77. ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
  • 78. የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
ሼር ያድርጉ
logo
logo
logo
logo
logo
  • 1.ورَةُ الْفَاتِحَة
  • 2.ورَةُ البقرة
  • 3.سُورَةُ آل عمران
  • 4.سورة النساء
  • 5.سورۃ المائدة
  • 6.سورة الأنعام
  • 7.سورة الاعراف
  • 8.سورۃ الانفال
  • 9.سورة التوبة
  • 10.سورة يونس
  • 11.سورۃ ھود
  • 12.سورة يوسف
  • 13.سورة الرعد
  • 14.سورة ابراهيم
  • 15.سورة الحجر
  • 16.سورة النحل
  • 17.سورة الإسراء
  • 18.سورة الكهف
  • 19.سورة مريم
  • 20.سورة طه
  • 21.سورة الأنبياء
  • 22.سورة الحج
  • 23.سورة المؤمنون
  • 24.سورة النور
  • 25.سورة الفرقان
  • 26.سورة الشعراء
  • 27.سورة النمل
  • 28.سورة القصص
  • 29.سورة العنكبوت
  • 30.سورة الروم
  • 31.سورة لقمان
  • 32.سورة السجدة
  • 33.سورة الأحزاب
  • 34.سورة سبإ
  • 35.سورة فاطر
  • 36.سورةيس
  • 37.سورة الصافات
  • 38.سورة ص
  • 39.سورة الزمر
  • 40.سورة غافر
  • 41.سورة فصلت
  • 42.سورة الشورى
  • 43.سورة الزخرف
  • 44.سورة الدخان
  • 45.سورة الجاثية
  • 46.سورة الأحقاف
  • 47.سورة محمد
  • 48.سورة الفتح
  • 49.ورة الحجرات
  • 50.سورة ق
  • 51.سورة الذاريات
  • 52.سورة الطور
  • 53.سورة النجم
  • 54.سورة القمر
  • 55.سورة الرحمن
  • 56.سورة الواقعة
  • 57.سورة الحديد
  • 58.سورة المجادلة
  • 59.سورة الحشر
  • 60.سورة الممتحنة
  • 61.سورة الصف
  • 62.سورة الجمعة
  • 63.سورة المنافقون
  • 64.سورة التغابن
  • 65.سورة الطلاق
  • 66.سورة التحريم
  • 67.سورة الملك
  • 68.سورة القلم
  • 69.سورة الحاقة
  • 70.سورة المعارج
  • 71.سورة نوح
  • 72.سورة الجن
  • 73.سورة المزمل
  • 74.سورة المدثر
  • 75.سورة القيامة
  • 76.سورة الانسان
  • 77.سورة المرسلات
  • 78.سورة النبإ
  • 79.سورة النازعات
  • 80.سورة عبس
  • 81.سورة التكوير
  • 82.سورة الإنفطار
  • 83.سورة المطففين
  • 84.سورة الإنشقاق
  • 85.سورة البروج
  • 86.سورة الطارق
  • 87.سورة الأعلى
  • 88.سورة الغاشية
  • 89.سورة الفجر
  • 90.سورة البلد
  • 91.سورة الشمس
  • 92.سورة الليل
  • 93.سورة الضحى
  • 94.سورة الشرح
  • 95.سورة التين
  • 96.سورة العلق
  • 97.سورة القدر
  • 98.سورة البينة
  • 99.سورة الزلزلة
  • 100.سورة العاديات
  • 101.سورة القارعة
  • 102.Aسورة التكاثر
  • 103.سورة العصر
  • 104.سورة الهمزة
  • 105.سورة الفيل
  • 106.سورة قريش
  • 107.سورة الماعون
  • 108.سورة الكوثر
  • 109.سورة الكافرون
  • 110.سورة النصر
  • 111.سورة المسد
  • 112.سورة الإخلاص
  • 113.سورة الفلق
  • 114.سورة الناس