• 1. መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
  • 2. መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
  • 3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
  • 4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
  • 5. የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
  • 6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
  • 7. አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
  • 8. ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
  • 9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
  • 10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
  • 11. ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
  • 12. ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
  • 13. በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
  • 14. ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
  • 15. ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
  • 16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
  • 17. «የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
  • 18. «አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
  • 19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
  • 20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
  • 21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
  • 22. (ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
  • 23. «ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
  • 24. «አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
  • 25. (ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
  • 26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
  • 27. የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
  • 28. (ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
  • 29. (አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
  • 30. «ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
  • 31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
  • 32. «ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
  • 33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
  • 34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
  • 35. እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
  • 36. እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
  • 37. አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
  • 38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
  • 39. ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
  • 40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
  • 41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
  • 42. ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
  • 43. በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
  • 44. ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
  • 45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
  • 46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
  • 47. በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
  • 48. እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
  • 49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
  • 50. የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
  • 51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
  • 52. «በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
  • 53. «በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
  • 54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
  • 55. ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
  • 56. ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
  • 57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
  • 58. (የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
  • 59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
  • 60. ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
  • 61. ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
  • 62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
  • 63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
  • 64. እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
  • 65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
  • 66. እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
  • 67. ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
  • 68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
  • 69. እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
  • 70. እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
  • 71. ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
  • 72. በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
  • 73. የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
  • 74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
  • 75. ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
  • 76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
  • 77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
  • 78. በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
  • 79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
  • 80. እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
  • 81. እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
  • 82. ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
  • 83. ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
  • 84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
  • 85. «ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
  • 86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
  • 87. «በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
  • 88. በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
  • 89. «እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
  • 90. ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
  • 91. ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
  • 92. «የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
  • 93. በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
  • 94. ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
  • 95. አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
  • 96. «አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
  • 97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
  • 98. በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
  • 99. አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
  • 100. ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
  • 101. ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
  • 102. ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
  • 103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
  • 104. ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
  • 105. ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
  • 106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
  • 107. በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
  • 108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
  • 109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
  • 110. እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
  • 111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
  • 112. በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
  • 113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
  • 114. በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
  • 115. እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
  • 116. ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
  • 117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
  • 118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
  • 119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
  • 120. ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
  • 121. እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
  • 122. ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
  • 123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
  • 124. ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
  • 125. በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
  • 126. አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
  • 127. አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
  • 128. ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
  • 129. በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
  • 130. ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
  • 131. እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
  • 132. እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
  • 133. ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
  • 134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
  • 135. (በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
  • 136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
  • 137. እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
  • 138. በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
  • 139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
  • 140. ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
  • 141. ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
  • 142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
  • 143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
  • 144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
  • 145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
  • 146. በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
  • 147. ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
  • 148. አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
  • 149. (የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
  • 150. ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
  • 151. ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
  • 152. «አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
  • 153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
  • 154. ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
  • 155. አትገነዘቡምን?
  • 156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
  • 157. «እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
  • 158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
  • 159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
  • 160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
  • 161. እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
  • 162. በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
  • 163. ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
  • 164. (ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
  • 165. እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
  • 166. እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
  • 167. እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
  • 168. «ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
  • 169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
  • 170. ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
  • 171. (የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
  • 172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
  • 173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
  • 174. ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
  • 175. እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
  • 176. በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
  • 177. በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
  • 178. እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
  • 179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
  • 180. የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
  • 181. በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
  • 182. ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
ሼር ያድርጉ
logo
logo
logo
logo
logo
  • 1.ورَةُ الْفَاتِحَة
  • 2.ورَةُ البقرة
  • 3.سُورَةُ آل عمران
  • 4.سورة النساء
  • 5.سورۃ المائدة
  • 6.سورة الأنعام
  • 7.سورة الاعراف
  • 8.سورۃ الانفال
  • 9.سورة التوبة
  • 10.سورة يونس
  • 11.سورۃ ھود
  • 12.سورة يوسف
  • 13.سورة الرعد
  • 14.سورة ابراهيم
  • 15.سورة الحجر
  • 16.سورة النحل
  • 17.سورة الإسراء
  • 18.سورة الكهف
  • 19.سورة مريم
  • 20.سورة طه
  • 21.سورة الأنبياء
  • 22.سورة الحج
  • 23.سورة المؤمنون
  • 24.سورة النور
  • 25.سورة الفرقان
  • 26.سورة الشعراء
  • 27.سورة النمل
  • 28.سورة القصص
  • 29.سورة العنكبوت
  • 30.سورة الروم
  • 31.سورة لقمان
  • 32.سورة السجدة
  • 33.سورة الأحزاب
  • 34.سورة سبإ
  • 35.سورة فاطر
  • 36.سورةيس
  • 37.سورة الصافات
  • 38.سورة ص
  • 39.سورة الزمر
  • 40.سورة غافر
  • 41.سورة فصلت
  • 42.سورة الشورى
  • 43.سورة الزخرف
  • 44.سورة الدخان
  • 45.سورة الجاثية
  • 46.سورة الأحقاف
  • 47.سورة محمد
  • 48.سورة الفتح
  • 49.ورة الحجرات
  • 50.سورة ق
  • 51.سورة الذاريات
  • 52.سورة الطور
  • 53.سورة النجم
  • 54.سورة القمر
  • 55.سورة الرحمن
  • 56.سورة الواقعة
  • 57.سورة الحديد
  • 58.سورة المجادلة
  • 59.سورة الحشر
  • 60.سورة الممتحنة
  • 61.سورة الصف
  • 62.سورة الجمعة
  • 63.سورة المنافقون
  • 64.سورة التغابن
  • 65.سورة الطلاق
  • 66.سورة التحريم
  • 67.سورة الملك
  • 68.سورة القلم
  • 69.سورة الحاقة
  • 70.سورة المعارج
  • 71.سورة نوح
  • 72.سورة الجن
  • 73.سورة المزمل
  • 74.سورة المدثر
  • 75.سورة القيامة
  • 76.سورة الانسان
  • 77.سورة المرسلات
  • 78.سورة النبإ
  • 79.سورة النازعات
  • 80.سورة عبس
  • 81.سورة التكوير
  • 82.سورة الإنفطار
  • 83.سورة المطففين
  • 84.سورة الإنشقاق
  • 85.سورة البروج
  • 86.سورة الطارق
  • 87.سورة الأعلى
  • 88.سورة الغاشية
  • 89.سورة الفجر
  • 90.سورة البلد
  • 91.سورة الشمس
  • 92.سورة الليل
  • 93.سورة الضحى
  • 94.سورة الشرح
  • 95.سورة التين
  • 96.سورة العلق
  • 97.سورة القدر
  • 98.سورة البينة
  • 99.سورة الزلزلة
  • 100.سورة العاديات
  • 101.سورة القارعة
  • 102.Aسورة التكاثر
  • 103.سورة العصر
  • 104.سورة الهمزة
  • 105.سورة الفيل
  • 106.سورة قريش
  • 107.سورة الماعون
  • 108.سورة الكوثر
  • 109.سورة الكافرون
  • 110.سورة النصر
  • 111.سورة المسد
  • 112.سورة الإخلاص
  • 113.سورة الفلق
  • 114.سورة الناس